You Are Here: Home > Other Forecasts > Forecast Viewer
 English አማርኛ

        
 

Bega 2021-22_outlook

 
   
 
Seasonal Print PDF

ባለፈው የክረምት ወቅት ለክረምት ዝናብ መጠናከርና መስፋፋት አስተዋጽኦ የሚያደረጉ አካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ገጽታዎች በከባቢ አየር ውስጥ ምቹ ሁኔታን በመፍጠራቸው የክረምት ዝናብ በወቅቱ ዝናብ ተጠቃሚ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከመደበኛዉ ጋር የተቀራራበ ዝናብ እንዲኖር ምክንያት ሆኗል። ያለፈው ክረምት ዝናብ በአገባብ ረገድ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ መደበኛውን ፈር የተከተለ ሲሆን፤ በአወጣጥ ረገድ ግን ከመካከለኛውና ከምሥራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ለተወሰኑ ቀናት መዘግየት አሳይቷል።

መጪው የበጋ ወቅት አማራ፣ ትግራይ፣ አፋር እንዲሁም የሰሜን ሶማሌና የቤኒሻኒጉል-ጉሙዝ ክልል፣ መካከለኛዉና ምስራቅ ኦሮሚያ አካባቢዎች ከመደበኛ ጋር የተቀራረበ ዝናብ የማግኘት ዕድል ከፍተኛ ሲሆን፤ በአንጻሩ የደቡብ አጋማሽ የቤኒሻኒጉል-ጉሙዝ፣ ምእራብ ኦሮሚያ፣ ጋምቤላ የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች አካባቢዎችን ጨምሮ መደበኛና ከመደበኛው በታች ዝናብ እንደሚኖራቸዉ የሚጠበቅ ሲሆን፤ የሶማሌ ደቡባዊ አጋማሽና የደቡብ ኦሮሚያ አካባቢዎች በአብዛኛው ከመደበኛው በታች ዝናብ እንደሚኖራቸዉ ይጠበቃል።

 PDF
Back to List



 
   
   

RSS Subscribe for Bulletins